የዝግጅት ሥነ ሥርዓት መጽሐፍ
()
About this ebook
ዳግ ሂዋርድ ሚልስ፣ በርካታ ተፈላጊ መጽሐፍ የጻፉና ከእነዚሁም ውስጥ “ታማኝነትና ታማኝ አለመሆን” የተባለው በዓለም ላይ ታዋቂ በሆነውን መጽሐፋቸው ይታወቃሉ። በአሁኑ ጊዜ ዩናይትድ ዲኖምኔሽን ኦርጂኔትድ ፍሮም ዘ ላይትሃውስ ግሩፕ ኦፍ ቸርች (United Denominations Originating from the Lighthouse Group of Churches) ተብሎ የሚጠራው ቤተ ክርስቲያን መስራች ናቸው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሶስት ሺህ ቤተክርስቲያኖች አሉት።
ዳግ ሂዋርድ ሚልስ፣ በዓለማቀፍ ደረጃ ወንጌላዊ ሲሆኑ “ፈዋሹ ኢየሱስ ክሩሴድ (HEALING JESUS CRUSADE) ” በተሰኘው እና በአለም ዙሪያ በተለያዩ ኮንፈረንሶች ላይ በአገልግሎታቸው ይታወቃሉ፡፡ ይበልጥ መረጃ ከፈለጉ ድህረ ገጻቸውን ይጎብኙ፣ www.daghewardmills.org.
Dag Heward-Mills
Bishop Dag Heward-Mills is a medical doctor by profession and the founder of the United Denominations Originating from the Lighthouse Group of Churches (UD-OLGC). The UD-OLGC comprises over three thousand churches pastored by seasoned ministers, groomed and trained in-house. Bishop Dag Heward-Mills oversees this charismatic group of denominations, which operates in over 90 different countries in Africa, Asia, Europe, the Caribbean, Australia, and North and South America. With a ministry spanning over thirty years, Dag Heward-Mills has authored several books with bestsellers including ‘The Art of Leadership’, ‘Loyalty and Disloyalty’, and ‘The Mega Church’. He is considered to be the largest publishing author in Africa, having had his books translated into over 52 languages with more than 40 million copies in print.
Related to የዝግጅት ሥነ ሥርዓት መጽሐፍ
Related ebooks
በውኑ በውሃውና በመንፈሱ ዳግም ተወልዳችኋልን? Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsበሥዕል የተደገፈ የዕባዳዎች አፈጻጸም ፍቅህ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsበዘፍጥረት ላይ የተሰጡ ስብከቶች (VI) - የሰውን ዘር ከጥፋት የሚያድን የወንጌል ምስክር ሁኑ (Amharic 54) Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsአደገኞች ልጆች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsላይኮስ ተኢው ስው እር አንልግኤት Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsሌሎች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsየጥንቱ ወንጌል ጥበብ (Amharic53) Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsውበት አውሬው እና መጋቢው Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsበዕብራውያን ላይ የተሰጡ ስብከቶች (I) - እምነታችሁን እንዴት ማጠንከር ትችላላችሁ? Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsትልቅ ቤተክርስቲያን Rating: 2 out of 5 stars2/5ቤተ ክርስቲያን ትከል Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsመንፈሳዊ አደጋዎች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsእውነታዊ ቁልፎች ለአዲስ አማኞች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsበየቀኑ ከእግዚአብሔር ጋር ውጤታማ የጥሞና ጊዜ ሊኖርህ ይችላል Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsየድል ሚስጢር Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsወደኋላ ማፈግፈግ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsሰይመው! ይገባኛል በል!! ውሰደ!!! Rating: 5 out of 5 stars5/5ዝንጉዎቹ Rating: 5 out of 5 stars5/5የሚከሱህ ሰዎች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsአገልግሎትህን አጉላው በመንፈስ ቅዱስ በሚደረግ ተዓምራትና መገለጦች Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsመልካም ጄነራል Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsየመጋቢነት አገልግሎትህን ወደ ላቀ ደረጃ አሳድግ Rating: 5 out of 5 stars5/5እንዴት ብርቱ ክርስቲያን ልትሆን ትችላለህ Rating: 5 out of 5 stars5/5እግዚአብሔርን ማገልገል ትልቅ ነገር ነው Rating: 4 out of 5 stars4/5ልጄ ሆይ ትችያለሽ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsእረኛ መሆን ምን ማለት ነው Rating: 5 out of 5 stars5/5የጸሎት ያለህ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsዛፉ እና አገልግሎትህ Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsከእናንተም አንዱ ዲያብሎስ ነው Rating: 0 out of 5 stars0 ratingsዳግም መወለድ ብሎም ገሃነምን ማስወገድ Rating: 0 out of 5 stars0 ratings
Reviews for የዝግጅት ሥነ ሥርዓት መጽሐፍ
0 ratings0 reviews
Book preview
የዝግጅት ሥነ ሥርዓት መጽሐፍ - Dag Heward-Mills
የስም ስያሜ ስነ ስርዓት ባህላዊ ኩነት ሲሆን ህጻን ልጅ ከተወለደ በኋላ የሚከናወን ነው፡፡ አንዳንድ ቤተሰቦች እጅግ ባህላዊ ከመሆናቸውም በላይ ከኩነቱ ጋር በተያያዘ በዕለቱ እና በጊዜው ይመራሉ፡፡ እዚህ ጋር የመጋቢው ሚና በዋናነት የክብረ በዓሉን መጽሐፍ ቅዱሳዊ እና መንፈሳዊ ይዘት ማስተዋወቅ ነው፡፡ በርግጥ ይህ በወላጆች ጥያቄ እና ፈቃድ መሰረት የሚወሰን ይሆናል፡፡
1. የመክፈቻ ጸሎት
2. አምልኮ፡ ኑና እርሱን እንውደድ
ኑና እርሱን እንውደድ እርሱ ብቻ የተገባው ነውና
ኑና እርሱን እንውደድ እርሱ ብቻ የተገባው ነውና
ኑና እርሱን እንውደድ እርሱ ብቻ የተገባው ነውና
ክርስቶስ ጌታን ክርስቶስ ጌታ
3. የስነ ስርኣቱ ምክንያት
ዛሬ በዚህ ከወንድማችን እና ከእህታችን፣ አቶ እና ወ/ሮ . . . (ሙሉ ስማቸው ይጠቀሳል) የተሰበሰብነው በሁለት ምክንያት ነው፤
1. እግዚአብሔር ባደረገላቸው ነገር ሃሴት ለማድረግ እና
እግዚአብሔር ባደረገላቸው ነገር ሃሴት ለማድረግ ማንኛውም ለምናደርገው ነገር መሰረት መጽሐፍ ቅዱስ ስለሆነ ለዛሬ የምናነበው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል፡
የኤልሳቤጥም የመውለጃዋ ጊዜ ደረሰ፥ ወንድ ልጅም ወለደች።
ጎረቤቶችዋም ዘመዶችዋም ጌታ ምሕረቱን እንዳገነነላት ሰምተው ከእርስዋ ጋር ደስ አላቸው።
በስምንተኛውም ቀን ሕፃኑን ሊገርዙት መጡ፥ በአባቱም ስም ዘካርያስ ሊሉት ወደዱ።
እናቱ ግን መልሳ። አይሆንም፥ ዮሐንስ ይባል እንጂ አለች።
እነርሱም፦ ከወገንሽ ማንም በዚህ ስም የተጠራ የለም አሉአት።
አባቱንም ማን ሊባል እንዲወድ ጠቀሱት።
ብራናም ለምኖ። ስሙ ዮሐንስ ነው ብሎ ጻፈ። ሁሉም አደነቁ።
ያንጊዜም አፉ ተከፈተ መላሱም ተፈታ እግዚአብሔርንም እየባረከ ተናገረ።
ሉቃ 1፡57-64
በዚያ ዘመን ይደረግ እንደነበረው እኛም የህጻኑን አባት መስጠት የፈለገውን የልጁ/ልጆቹ ስም/ስሞች እና ትርጉሙን/ትርጉማቸውን እንዲናገር እድል እንሰጣለን፡፡
4. ስም በአባት ይሰጣል (አባት ይነሳና የልጁን/ልጆቹን ሙሉ ስም እንዲሁም ትርጉሙን/ትርጉማቸውን ይናገራል)
5. የልጁ ስም ይታወጃል፣ ይቀደሳል ይጸናል
1. አገልጋዩ ወስዶ ህጻኑን ከታቀፈ በኋላ ታዳሚውን ሁሉ እንዲቆሙ ይጠይቃል፡፡
2. አገልጋዩ በህጻኑ ላይ እጁን ጭኖ ከጸለየ በኋላ ዘይት ይቀባዋል፡፡
6. ጸሎት
አገልጋዩ፡ አባት ሆይ በአንድያ ልጅህ በኢየሱስ ስም ዛሬ ስለተሰጠው ስም/ስሞች እናመሰግንሃለን፡፡ ይህንን/እነዚህን ስም/ስሞች እንቀድሳለን እናም የልጁ ስም/ስሞች . . . በማለት እናውጃለን… ከዛሬ ጀምሮ የስሙን ትርጉም መኖር እንዲችል እጸልያለሁ፡፡
አገልጋዩ የልጁን ስም በማውሳት የስሙን ዓላማ መኖር እንዲችል ይጸልይለታል፡፡ (ለምሳሌ፡ ዮሐንስ˝ ማለት
ያህዌ ቸር ነው˝ ማለት ሲሆን ለዚህ ህጻን ሁልጊዜም ያህዌ ቸርነት ያድርግለት˝)
አገልጋይ፡ ይህንን ህጻን የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ በሆነው በዘይት እቀባዋለሁ፤ በዚህም በህይወት ዘመኑ ሁሉ በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ስር ይሆን ዘንድ ነው፡፡ አሜን፡፡
7. መዝሙር፡ የበረከት ዝናብ
የበረከት ዝናብ ይሆናል፤ የበረከት ዝናብ
ይህ የአምላክ ተስፋ ነው፤ የምንለምነው የበረከት ዝናብ
የመታደስ ዘመን ይሆናል፤ የምህረቱ ጠል ይንጠባጠባል
ከላይ ከአዳኙ የሚመጣ/ የምንለምነው ዝናብ
8. ለህጻኑ ቡራኬ የመስጠት ጊዜ
አገልጋዩ፡ አባት ሆይ በጎ እና ፍጹም ስለሆነው ስለ ህይወት ስጦታ በርግጥ እናመሰግንሃለን፡፡ ይህንንም ቤተሰብ በዚህ ልጅ ስለባረካቸው ተመስገን፡፡ በዚህ ልጅ ህይወት እና ስም ላይ የሚሰነዘር ማናቸውንም መርገም እና የጠላት ሃሳብ እሰርዛለሁ፣ አመክናለሁ፣ እገለብጣለሁ እንዲሁም አስወግዳለሁ፡፡
በዚህ ልጅ ህይወት እና ስም ላይ ከፍ የሚልን ማናቸውም የሚቋቋም የተቃውሞ ምሽግ፣ ተገዳዳሪ፣ አስጨናቂ ነገርን ሁሉ አፈርሳለሁ፡፡ በዚህ ህጻን ህይወት ላይ ጠላት ባቀደው፣ ባለመውና ባነጣጠረው ፈንታ የእግዚአብሔርን ፈቃድ እንዲበረታ እና እንዲያይል ጸለይኩ፡፡
በህይወትህ ላይ የእግዚአብሔርን ፈቃድ እናገራለሁ፡፡
በህይወትህ ዘመን ሁሉ የእግዚአብሔር በጎነትና ሞገስ እድል ፈንታህ ይሁን፡፡
ለወላጆችህ በረከት ሆነህ ኑር፡፡
ለትውልድህ በረከት ሆነህ ኑር፡፡
እግዚአብሔር እንድትሆን የወሰነውን ሁን፡፡ ብርቱ በሆነው በኢየሱስ ስም፡፡ አሜን፡፡
9. ማሳሰቢያ ለወላጆች
አገልጋዩ፡ ይህ ህጻን ባደገ ጊዜ ፈቀቅ እንዳይል በጌታ መንገድ በመምራት ለማሳደግ ቃል ትገባላችሁን?
በዘዳግም 6፡7 መሰረት "የእግዚአብሔርን ቃል በቤት ስትቀመጡ ፣በመንገድ ስትሄዱ፣ ስትተኙም፣ ስትነሱም ልታስተምሩት ቃል ትገባላችሁን?˝
አባት፡ አዎን፡፡
እናት፡ አዎን፡፡
ሁለቱም ወላጆች በጋራ፡ አዎን፡፡
አገልጋዩ፡ አሜን! እናጨብጭብላቸው! (አገልጋዩ ልጁን ለወላጆቹ ይመልሳል)
10. መዝሙር፡ ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን
ለእግዚአብሔር ክብር ይሁን ጌታ ይመስገን! ጌታ ይመስገን
ታላቅ ነገር አድርጓል ምድር ድምጹን ትስማ
አለምን ስለወደደ ጌታ ይመስገን! ጌታ ይመስገን!
ልጁን ሰጠን ህዝቦች ደስ ይበላቸው
እርሱም ህይወቱን ሰጠን ኦ ወደ አብ በልጁ በኢየሱስ ኑ
ለሐጢያታችን